| Ethio-Australian sports festival - Dec, 2011 |
« ስፖርት ማለት የአማተር ስፖርት ነው። አማተር ማለት ስፖርትን ለጥቅም ማግኛ ሳይሆን ሰውነቱንና አዕምሮውን ለማሻሻል ጤነኛ የጊዜ ማሳለፊያ ለማግኘት ብቻ ሲል የሚያዘወትረው ነው። ስፖርት በዛሬው ዘመን ሥልጣኔ በተለይ የሰውን አካል አሳምሮ የሚቀርፅና ጤንነቱን ለመጠበቅ ኃይል የሚሠጠው አብነት ነው። ባስተዳደግ ረገድ ደግሞ ልጆችንና ወጣቶችን እውነተኛ በሆነና ሥርአትን በሚከተል መንገድ በጋለ መንፈስ መወዳደርን ስለሚያስተምራቸው ለወደፊቱ ለሰብዓዊና ለማህበራዊ ኑሮአቸው የሚዘጋጁበት ታላቅ የአስተዳደግ መሳሪያ ሆኖ ተገኝቷል። ስፖርትን ማዘውተር አካልን ብቻ ሳይሆን ነፍስንም ጭምር የሚያንፅ ነው። ሳያውቁትና ሳይገነዘቡት የመንፈስ ቅንነትን፤ ደፋርነትን፤ ብርታትን፤ ራስ መግዛትን፤ ቆራጥነትን፤ የቡድን መንፈስን የሚያጎለምስ ነው። » ይድነቃቸው ተሰማ ከ'የፒያሳ ልጅ' በፍቅሩ ኪዳኔ የተወሰደ |
| Schedules & Info. Tables |
|
